የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም በተሰራው ሪፎርም ላይ ተንተርሶ በመጡት ለውጦች ምክንያት ከተለያዩ ተቋማት ጋር በጋራ የመስራት እድሎች እየፈጠረ እንደሚገኝ እና ከዓለም የፖስታ አገልግሎቶች የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ ሽልማቶችን የተቀበለበት ሁኔታ እንዳለ አብራርተዋል፡፡

አቶ ዳግማዊ ቴክኖሎጂውን በሚገባ ከመጠቀም እና ተደራሽነትን ከማስፋት አንጻር የኢትዮጵያ ፖስታ በቅርቡ ዝግጅታቸውን አጠናቆ ወደ ስራ ሊያስገባቸው ያቀዳቸውን የኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ እና የቨርቹዋል ፖስታ አገልግሎቶች በተመለከተ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

በተያያዘም አገልግሎቶቹ በሚወጡበት ጊዜ ከምንም በላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ለደንበኞቹ ቅርብ የሚሆንበትን አሰራር ለመዘርጋት የሚያስችል እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »