የኢትዮጵያ ፖስታ የታዳጊዎችን የደብዳቤ ፅሁፍ ውድድር በደማቅ ሁኔታ አጠናቋል።

አለም አቀፍ የሙዚየም ቀን አከባበርን በማስቀጠል የኢትዮጵያ ፖስታ የታዳጊዎችን የደብዳቤ ፅሁፍ ውድድር የመዝጊያ ዝግጅት በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል። በውድድሩ ተሳትፈው ከአንድ እስከ ሶስት ለወጡ ታዳጊዎች የኢትዮጵያፖስታ የታብሌት ሽልማት አበርክቷል። ይህ ዝግጅት ተስፋቸውን እና ህልማቸውን የሚገልጹ ወጣት ተሰጥኦዎችን ጊዜ በማይሽረው የደብዳቤ ጽሑፍ ጥበብ አጉልቶ ያሳየ ነበር።  “ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ እናግኝ” በሚል ርዕስ የተካሄደው ውድድር ይህን ዘርፈ ብዙ ችግር መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል።

በዝግጅቱ ላይ ዋና ኮሜርሻል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በኢትዮጵያ ፖስታ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ ለታዳሚዎች ገለፃ በማድረግ ለፈጠራ እና ለደንበኞች እርካታ ያለንን ቁርጠኝነት አሳይተዋል።  በተጨማሪም የፖስታ ሙዚየም ሱፐርቫይዘር አቶ ደረጀ ሁሉንም ታዳሚ የኢትዮጵያፖስታ ሙዚየምን አስጎብኝተዋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »