የኢትዮጵያ ፖስታ የታዳጊዎችን የደብዳቤ ፅሁፍ ውድድር በደማቅ ሁኔታ አጠናቋል።

አለም አቀፍ የሙዚየም ቀን አከባበርን በማስቀጠል የኢትዮጵያ ፖስታ የታዳጊዎችን የደብዳቤ ፅሁፍ ውድድር የመዝጊያ ዝግጅት በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል። በውድድሩ ተሳትፈው ከአንድ እስከ ሶስት ለወጡ ታዳጊዎች የኢትዮጵያፖስታ የታብሌት ሽልማት አበርክቷል። ይህ ዝግጅት ተስፋቸውን እና ህልማቸውን የሚገልጹ ወጣት ተሰጥኦዎችን ጊዜ በማይሽረው የደብዳቤ ጽሑፍ ጥበብ አጉልቶ ያሳየ ነበር።  “ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ እናግኝ” በሚል ርዕስ የተካሄደው ውድድር ይህን ዘርፈ ብዙ ችግር መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል።

በዝግጅቱ ላይ ዋና ኮሜርሻል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በኢትዮጵያ ፖስታ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ ለታዳሚዎች ገለፃ በማድረግ ለፈጠራ እና ለደንበኞች እርካታ ያለንን ቁርጠኝነት አሳይተዋል።  በተጨማሪም የፖስታ ሙዚየም ሱፐርቫይዘር አቶ ደረጀ ሁሉንም ታዳሚ የኢትዮጵያፖስታ ሙዚየምን አስጎብኝተዋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »