የኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ዲጂታል የገበያ ማዕከልን ለማቅረብ ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ከሲኤስኤም አፍሪኮም ጋር በጋራ ተፈራርሟል።

በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሃገር ውስጥ እና አለም አቀፍ ዲጂታል የገበያ እድል ለመፍጠር የተዘጋጀው ፕሮጀክት፥ በዛሬው እለት ለየኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ዲጂታል የገበያ ማእከልን ለማቅረብ በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ስር የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ሲ.ኤስ.ኤም ከአፍሪኮም ጋር በጋራ በመሆን በዛሬው እለት ተፈራርመዋል። የኢትዮጵያ ፖስታ ይህን የኢ-ኮሜርስ ዲጂታል የገበያ ማእከልን በመምራት ብሎም የሎጂስቲክስ ክፍተቱን በመሙላት እንከን የለሽ እና ቀልጣፋ የአገልግሎት አቅርቦትን ለማረጋግጥ የሚሰራ ይሆናል።

ይህ ፕሮጀክት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በመደገፍ የኢ-ኮሜርስ መልክዓ ምድሩን ለመለወጥ በማለም የላቀ እርምጃ ወደፊት ያራምዳል። ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ጠንካራ የገበያ ቦታ በመፍጠር ለዳበረ ዲጂታል ኢኮኖሚ መንገድም ይከፍታል።

Follow us on our social media platforms | Facebook | Telegram | LinkedIn | Twitter | Instagram | Pinterest | TikTok |

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር የመገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቢረዳ እንዲሁም የንብረት አስተዳደር ክፍል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ይፍቱስራ መኮንን መገልገያ ቁሳቁሶቹን ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያስረከቡ ሲሆን የመቄዶኒያ አረጋዉያን የቡራኬ ስነስርዓት አድርገዋል።

Read More »
News

የ2024 የእስያ ፊላቴሊክ ኤግዚቢሽን በቻይና።

በሻንጋይ የተካሄደው የ2024 የኤዥያ አለም አቀፍ የቴምብር ኤግዚቢሽን የእስያን ባህል በፊላቴሊ ጥበብ የሚያሳይ ደማቅ በዓል ነበር። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች አስደናቂውን የቴምብር ማሳያ አድንቀዋል፣ እያንዳንዱም የቴምብር ስራዎች ታሪክን፣ ጥበብን እና ወግን ይናገራሉ።

Read More »
News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »