በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም የዘንድሮውን የ132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ልዩ የሚያደርገው የኢትዮጵያ ፖስታ በ2025 ከአፍሪካ በ ኢ.ኤም.ኤስ የአገልግሎት ጥራት አሸናፊ እንዲሁም ከዓለም 6ኛ ደረጃ መያዙ በታወቀበት ወቅት መከበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም ድርጅቱ በዘመናዊ አገልግሎት፣ በደንበኛ ተኮር አስተዳደር እና በአገልግሎት ጥራትም ጭምር እየተሻሻለ መምጣቱን ያሳያል ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የ132ኛ ዓመቱን በማስመልከት የተለያዩ ዲፓርትመንቶች ዋና የሥራ ኃላፊዎች በለፉት 3 ዓመታት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶችን በተመለከተ ለዝግጅቱ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በተጨማሪም በዕለቱ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር ወ/ሮ ትእግስት በቀለ የተመራ የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን በውይይቱም ላይ የሴቶች ውስጣዊ ጥንካሬ፣ አይበገሬ ማንነት እና የ“እችላለሁ” መንፈስ በተግባር ተገልጿል፡፡















