የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።

በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በውይይቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ በአምስቱ ዋና ዋና የስትራቴጂክ ምሰሶዎችን መሰረት ባደረጉ አፈጻጸሞች እና ቀጣይ እቅዶች ላይ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በሰው ሀብት አስተዳደር ዙርያ የሚኖሩ የተለያዩ የአሰራር ማሻሻያዎችም እንዲሁ ሰፊ ገለጻ ተደርጎባቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በሁለተኛው ምዕራፍ ላይ ከሰራተኞች ለተነሱት አጠቃላይ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሾችን የሰጡ ሲሆን በውይይቱ መጠናቀቂያም ድርጅቱ እያስመዘገበ ላለው ዘርፈ ብዙ ስኬት ዋና ባለቤት ሰራተኛው መሆኑን ገልጸው፤ ሁሉን አቀፍ እድገት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሆነ እና የቀጣይ በጀት ዓመት ግቦችን በጋራ ለማሳካት የሁሉም ሰራተኞች አስተዋጾ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ የአየር ኃይላችንን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጃቸውን አራት አይነት ታሪካዊ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።

ዛሬ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተመሰረተበትን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አክብሯል። የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ ለመዘከር ያሳተማቸውን አራት አይነት ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በይፋ አስመረቀ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ያበለጸጋቸውን የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመርቋል፡፡

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »