Ethiopost Receives the 2023 Postal Excellence Award

Ethiopost receives the 2023 Postal Excellence Award in Riyadh as the lead for the Africa Region! Our Deputy CEO, Gashaw Mersha, had the honor of receiving the award on our behalf.

This recognition is the result of Ethiopost’s exemplary performance across key metrics evaluating designated postal operators. These past few years, Ethiopost has been hard at work implementing institutional reforms that address service quality, delivery, speed, and accessibility, among many others. We are proud that this effort has culminated in this recognition as a regional leader in postal excellence by the Universal Postal Union’s Extraordinary Congress held in Riyadh, Saudi Arabia.


የኢትዮጵያፖስታ በሪያድ የአፍሪካ ሪጅን የPostal Excellence Award ተሸላሚ ሆነ!

የዓለም ፖስታ ሕብረት በየዓመቱ በሚያደርገው የፖስታ አገልግሎት ሰጪዎች ምዘና የኢትዮጵያ ፖስታ በ2023 ዓ.ም. የአፍሪካ ሪጅን አሽናፊ መሆኑ ተገለጸ። ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጋሻው መርሻ ሽልማቱን ተቀብለዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ባለፉት ዓመታት ተቋማዊ ሪፎርሞችን በመተግበር የአገልግሎት አሠጣጥ ማሻሻያዎች፣ የመልዕክት ፍጥነትና ተደራሽነት ላይ በርካታ ለውጦች እንዳመጣ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የዓለም ፖስታ ሕብረት በሚያደርገው የአግልግሎት ጥራት ምዘና ከዓመት ዓመት አፈጻጸሙን ሲያሻሽል ቆይቶ ዛሬ በሪያድ፣ ሳውዲ አረቢያ በተደረገው የሕብረቱ ልዩ ኮንግረስ ላይ የአፍሪካ ሪጅንን በመምራት የፖስታ ልሕቀት ሽልማት ተቀብሏል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር የመገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቢረዳ እንዲሁም የንብረት አስተዳደር ክፍል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ይፍቱስራ መኮንን መገልገያ ቁሳቁሶቹን ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያስረከቡ ሲሆን የመቄዶኒያ አረጋዉያን የቡራኬ ስነስርዓት አድርገዋል።

Read More »
News

የ2024 የእስያ ፊላቴሊክ ኤግዚቢሽን በቻይና።

በሻንጋይ የተካሄደው የ2024 የኤዥያ አለም አቀፍ የቴምብር ኤግዚቢሽን የእስያን ባህል በፊላቴሊ ጥበብ የሚያሳይ ደማቅ በዓል ነበር። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች አስደናቂውን የቴምብር ማሳያ አድንቀዋል፣ እያንዳንዱም የቴምብር ስራዎች ታሪክን፣ ጥበብን እና ወግን ይናገራሉ።

Read More »
News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »