News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በይፋ አስመረቀ፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ያበለጸጋቸውን የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመርቋል፡፡

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ውሎች ዝግጅት በኢትዮጵያ ፖስታ
የኢትዮጵያ ፖስታ ከሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት በተሰጠው ውክልና መሰረት የውል ጽሁፎችን በማሰናዳት እናንተን ለማገልገል ከዛሬ ሐምሌ 1 ፣ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተመረጡ ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት ጀምራል።

የኢትዮዽያ ፖስታ በስኬት ጉዞ ላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጹ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቆይታ ለውጡን ተከትሎ በተሰሩ ተከታታይ የሪፎርም ሥራዎች የኢትዮጵያ ፖስታ ከነበሩበት ችግሮች ተላቆ በብዙ የስራ ትጋትና ጥረት በአንዳንድ አገልግሎቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመወዳደር የሚያችል አቅም እንደገነባ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ግንቦት 14 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሄደው የዲጂታል ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ወርክሾፕ ላይ ተሳተፈ።

የዓለምአቀፍ የፖስታ ህብረት በፖሰታ አባል አገራት መካከል ለሚደረግ የፖስታ መልዕክቶች ልውውጥ የክፍያ ስርዓት በተመለከተ ለስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ሥልጠና ሰጠ፡፡
የዓለምአቀፍ የፖስታ ህብረት በፖሰታ አባል አገራት መካከል ለሚደረግ የፖስታ መልዕክቶች ልውውጥ /UPU Remuneration System/ የክፍያ ስርዓት በተመለከተ ለስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ሥልጠና ሰጠ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።
የስምምነቱ ዋና አላማ የመንገድ ፈንድ እድሳትን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የአገልግሎት መስጫ ቅርንጫፎች እና በዓመታዊ የተሽከርካሪ ቴክኒክ ደህንነት ምርመራ ተቋማት እንዲኖር ማድረግ ሲሆን ሁሉንም አገልግሎት በአንድ ቦታ መስጠት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮዽያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎች ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የበላይ አመራሮች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።
የኢትዮዽያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎች ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የበላይ አመራሮች ጋር በቀጣይ በጋራ መስራት በሚቻለባቸው ጉዳዮች ላይ በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።
