የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

የስምምነቱ ዋና አላማ የመንገድ ፈንድ እድሳትን በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ከአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን የአገልግሎት መስጫ ቅርንጫፎች እና በዓመታዊ የተሽከርካሪ ቴክኒክ ደህንነት ምርመራ ተቋማት እንዲኖር ማድረግ ሲሆን ሁሉንም አገልግሎት በአንድ ቦታ መስጠት የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም የአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን የኢትዮጵያ ፖስታ ሕጋዊ ውክል ባለው የመንገድ ፈንድ ሰርተፍኬት እድሳት ስራ ላይ በባለስልጣኑ አገልግሎት መስጫ ቅርንጫፎች በመገኘት ተጨማሪ ደንበኞች አገልግሎቱን ማግኘት እንዲችሉ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡

ይህ ስምምነት አገልግሎት አሰጣጡንና የመረጃ አያያዝ ስርዓትን በማዘመን የደንበኞችን የአገልግሎት እርካታ እንደሚጨምር የታመነ ሲሆን ጥናትና የአሰራር ማሻሻያ በማካሄድ ዉጤታማ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ብቃት የማረጋገጥ ተልዕኮ  ያለው እንደሆነም በስብሰባው ላይ ተገልጿል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »