የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!

በ 1967 ዓ.ም የተቋቋመው ታሪካዊው የፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመቱን በዛሬው እለት በድምቀት አክብሮ ውሏል፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች እና ታላላቅ የሃገራችን ሰአሊያን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም በፖስታ ሙዚየሙ ላይ ሊሠሩ ከታቀዱት የማስፋፊያ ሥራዎች አኳያ የባለድርሻ አካላቱ ሃሳብ እና እገዛ እንደሚያስፈልግ እና በብዙ መልኩ ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ መሆኑንም ጠቅሰው ለታዳሚው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የፖስታ ሙዚየሙ ሱፐርቫይዘር የሆኑት አቶ ደረጀ ብርሃኑ ለተሳታፊዎቹ በሙዚየሙ ውስጥ ያሉትን 50 ዓመታትን ያስቆጠሩ የቴምብር ሥራዎችን አስጎብኝተው በቅርቡ በካታሎግ መልክ ተዘጋጅተው ለጎብኚዎች እንዲደርሱ ለማድረግ እየተሠራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዚሁ ክብረ በዓል ላይ የተገኙ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ማለትም አቶ አሰፋ ጉያ፣ የሰዓሊ ቦጋለ በላቸው ቤተሰቦች እንዲሁም ሌሎች አንጋፍ አርቲስቶች በመድረኩ ላይ የፖስታ ሙዚየሙ አሁን ላለበት ደረጃ መድረስ በየደረጃው ያሉ የኢትዮጵያ ፖስታ የስራ መሪዎችን አመስግነው ሙዚየሙን ለማዘመን እና ለማስፋፋት በሚደረገው ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ከኢትዮጵያ ፖስታ ጎን በመቆም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል፡፡

በመጨረሻም የፖስታ ሙዚየሙ የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል በቀጣይም ለአንድ ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ እንደሚቀጥል እና ጎብኚዎችም መጥተው እየጎበኙ የዚህ ታሪክ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »