የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተደረሰው ስምምነት እንደተቋም በኢትዮጵያ ፖስታ የሶስት ዓመት ስትራቴጂክ ፕላን ላይ ትልቅ እመርታን የሚያመጣ መሆኑን ገልፀው በቅርቡ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል። በዝግጂቱ ላይ የኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ይለበስ አዲስም በበኩላቸው ተቋማቸው ከኢትዮጵያ ፖስታ ጋር ይሕን ስምምነት በማድረጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው የኦን ላይን ግብይት አከፋፈል ስርአቱን እና የውክልና ባንኪንግ ስራን (agency banking ) በእጅጉ ሊያግዝ የሚችል እንደሚሆን ገልፀዋል።

በተያያዘም ይህን ስምምነት ከታለመለት ግብ ለማድረስ የማስፈጸሚያ ሰነድ ( functional specification document ) በኢትዮጵያ ፖስታ ቺፍ ኮመርሺያል ኦፊሰር ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ እና በኢትስዊች ቺፍ ፖርቲፎሊኦ ኦፊሰር አቶ አቤኔዘር ላቀው በኩል ተፈርሟል። መጨረሻም በሁለቱም ተቋማት በኩል ለዚህ ስምምነት መሳካት ጥረት ያደረጉ አካላት ምስጋና ተችሯቸዋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »