የኢትዮጵያ ፖስታ ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ለመቄዶኒያ አበረከተ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት አንድ አካል አድርጎ በተለያዩ ዙሮች ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ዛሬም ይህን መልካም ተግባሩን በማስቀጠል፣ ግምታቸው 1,424,500.00 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሃያ አራት ሺህ አምስት መቶ) ብር የሆኑ ልዩ ልዩ ድጋፎችን ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል አስረክቧል።

ለተቋሙ የተደረገው ይህ ሰብአዊ ድጋፍ ልዩ ልዩ አልባሳትን፣ የሃይማኖት መጻሕፍትን እና ሌሎች ለተረጂዎች አስፈላጊ የሆኑ ቁሶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የሰው ሀብት አስተዳደር ቺፍ ኦፊሰር አቶ ተሾመ ቢረዳ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ማህበራዊ ግዴታውን ለመወጣት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። አቶ ተሾመ አክለውም፣ ድርጅቱ ከገንዘብ እርዳታ ባለፈ በቁሳቁስ ጭምር የሚያደርገው ድጋፍ በቀጣይነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም በዕለቱ የድጋፍ ርክክቡ በሚከናወንበት ወቅት በማዕከሉ በሚረዱ አባቶችና እናቶች የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »