የኢትዮጵያ ፖስታ ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ለመቄዶኒያ አበረከተ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት አንድ አካል አድርጎ በተለያዩ ዙሮች ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ዛሬም ይህን መልካም ተግባሩን በማስቀጠል፣ ግምታቸው 1,424,500.00 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሃያ አራት ሺህ አምስት መቶ) ብር የሆኑ ልዩ ልዩ ድጋፎችን ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል አስረክቧል።

ለተቋሙ የተደረገው ይህ ሰብአዊ ድጋፍ ልዩ ልዩ አልባሳትን፣ የሃይማኖት መጻሕፍትን እና ሌሎች ለተረጂዎች አስፈላጊ የሆኑ ቁሶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የሰው ሀብት አስተዳደር ቺፍ ኦፊሰር አቶ ተሾመ ቢረዳ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ማህበራዊ ግዴታውን ለመወጣት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ብለዋል። አቶ ተሾመ አክለውም፣ ድርጅቱ ከገንዘብ እርዳታ ባለፈ በቁሳቁስ ጭምር የሚያደርገው ድጋፍ በቀጣይነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም በዕለቱ የድጋፍ ርክክቡ በሚከናወንበት ወቅት በማዕከሉ በሚረዱ አባቶችና እናቶች የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »