የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን ከሰራተኞች ጋር በተለያዩ ከተሞች ለቀናት የቆየ ስብሰባ አድርጓል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን ከሰራተኞች ጋር በድሬዳዋ፣ በደሴ፣ ሀዋሳ፣ በጅማ እና መቀሌ ከተሞች ለቀናት የቆየ ስብሰባ አድርጓል፡፡ በስብሰባው የድርጅቱን የሶስት አመታት ስትራቴጂ የማጋራት እና የግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማን መሪ አካል ያደረገ ነበር።  ስብሰባው  ተቋሙ አሁንም በልህቀት እና በቅልጥፍና ስራውን እንዲቀጥል የሚያበረታታ እንደነበር ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤት፣ አጠቃላይ ፖስታ ቤት እና የማዕከላዊ ወረዳ ቅርንጫፎች የግማሽ አመታዊ አፈፃፀምን በተመለከተ የተደረገው ስብስባ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።

በድሬዳዋ ከተማ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ከተደረገው ውይይት የተወሰዱ ምስሎች ።

በደሴ እና ሀዋሳ ከተማ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ከተደረገው ውይይት የተወሰዱ ምስሎች ።

በጅማ እና መቀሌከተማ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ከተደረገው ውይይት የተወሰዱ ምስሎች ።

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »