የኢትዮጲያ ፖስታ አመራር አባላት የሶስት አመት ስትራቴጂክ እቅዱን ለዋና ዋና ባለድርሻ አካላት አቀረበ፡፡

የኢትዮጲያ ፖስታ አመራር አባላት የሶስት አመት ስትራቴጂክ እቅዱን ለዋና ዋና ባለድርሻ አካላት ያቀረበ ሲሆን ከነዚህም መካከል የገንዘብ ሚኒስቴር ተወካዮች፣ የመንግስት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ እና የሚመለከታቸው የፓርላማ ንዑስ ኮሚቴ አባላትን ያካትታል። ስብሰባው ተቋሙ ግቡን ለመምታት  ያጋጠሙት ተግዳሮቶች ላይ ወሳኝ ውይይት እንዲደረግበት ያደረገ ሲሆን ገንቢ አስተያየቶችን በማሰባሰብ ከባለ ድርሻ አካላት ለድርጅቱ ዓላማ ድጋፍ ለመስጠት ቃል ተገብቷል።

ከውይይቱ በኋላ የኢትዮጲያ ፖስታ አመራር እና ቦርድ የድርጅቱን የስድስት ወራት አፈጻጸም ገምግሟል።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »