Ethiopost engaged in a transformative meeting with Ethiopian Airlines

ቁልፍ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በመላው አፍሪካ የፖስታ እና የአቪዬሽን አገልግሎቶች ዘርፍ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል መድረክ ተዘጋጅቷል። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ አቤል አለሙ ጋር በጋራ በመሆን በመላው አህጉር የፖስታ አገልግሎቶችን ለማስጀመር፣ ለማስፋፋት እንዲሁም ለማጠናከር የሚረዱ ስልቶች ላይ በጋራ ለመዳሰስ እድሉን አግኝተናል። ይህ ጥምረት በአህጉር ደረጃ የፖስታ አገልግሎቶችን ውጤታማነት፣ አስተማማኝነት እና የአገልግሎት መሳለጥን የሚያሻሽል ስርዓት ለመፍጠር ያለመ ነው።

In a transformative meeting, Ethiopost engaged with H.E Dr. Sifundo Chief Moyo, Secretary General of PAPU, and Ato. Abel Alemu, MD of Ethiopian Airlines Cargo. This strategic collaboration envisions elevating postal and logistic services across Africa, fostering efficiency, reliability, and interconnectedness.

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »