የኢትዮጵያ ፖስታ በ2016 ዓ.ም እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል!

የኢትዮጵያ ፖስታ በ2016 ዓ.ም “የምትተክል አገር፣የሚያፀና ትውልድ!” በሚል መሪ ሀሣብ እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል!

በትናንትናው ዕለት በተካሄደው መርሃግብር ላይ በዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ መሪነት ከድርጅቱ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን ጋር በመሆን ዛፎችን በተመረጡ ቦታዎች በመትከል ለአረንጓዴ አሻራ አስተዋፅዖ አድርጓል። ይህ ተግባር የኢትዮጵያ ፖስታ ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ብቻ ሳይሆን የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ያለውን አስተዋጽኦ እና ጠቀሜታ አጉልቶ የሚያሣይ ነው።

 ለቀጣይ ትውልድ አረንጓዴ እና ከአየር ንብረት መዛባት የፀዳ ከባቢን እንፍጠር!

#green_legacy

#Ethiopost

#የምትተከል_አገር_የሚያፀና_ትውልድ!

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር የመገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቢረዳ እንዲሁም የንብረት አስተዳደር ክፍል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ይፍቱስራ መኮንን መገልገያ ቁሳቁሶቹን ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያስረከቡ ሲሆን የመቄዶኒያ አረጋዉያን የቡራኬ ስነስርዓት አድርገዋል።

Read More »
News

የ2024 የእስያ ፊላቴሊክ ኤግዚቢሽን በቻይና።

በሻንጋይ የተካሄደው የ2024 የኤዥያ አለም አቀፍ የቴምብር ኤግዚቢሽን የእስያን ባህል በፊላቴሊ ጥበብ የሚያሳይ ደማቅ በዓል ነበር። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች አስደናቂውን የቴምብር ማሳያ አድንቀዋል፣ እያንዳንዱም የቴምብር ስራዎች ታሪክን፣ ጥበብን እና ወግን ይናገራሉ።

Read More »
News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »