የኢትዮጵያ ፖስታ ከቶፓን ግራቪቲ ኢትዮጵያ ጋር አብሮ የመስራት ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም National ID Ethiopia አካል የሆነውን የፋይዳ መታወቂያ ካርድ የአቅርቦት አቅምንና ስርዓትን ለማሳደግ የአጋርነት ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና የቶፓን ግራቪቲ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ት ቃልኪዳን አረጋ ዛሬ የፈረሙ ሲሆን ይህ የሥራ ስምምነት ጥራቱን የጠበቀና አስተማማኝ የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ለነዋሪዎች በተቀላጠፈና በዘመነ መልኩ ለማቅረብ የሚያስችል ነው።

በተጨማሪም እያደገ የመጣውን የማህበረሰባችን የፋይዳ መታወቂያ ካርድ ፍላጎት ለማሟላትና ሁሉን አቀፍ እና አካታች የሆነውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዓላማ ለማሳካት የበኩላችንን አስተዋፅዖ ለማድረግ ያለንን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »