የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል። በጉብኝታቸውም ወቅት በድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ስለ ድርጅቱ አሁናዊ የስራ ክንውንና በቀጣይ ሊተገበሩ የታቀዱ የሪፎርም ሥራዎች ላይ ሰፊ ገለፃ የቀረበ ሲሆን በኢትዮጵያ ፖስታ ዋናው መስሪያ ቤት የተሰሩ የሕንጻ እድሳት ስራዎችን ፣ የህጻናት ማቆያ ፣ ከጥሪ ማእከል ፣ ከመልእክት መቀበል እስከ እደላ ያሉ የኦፕሬሽን ስራዎችን ከሙያዊ ማብራሪያ ጋር ጎብኝተዋል። ከዋናው መስሪያ ቤት በተጨማሪም በአራት ኪሎ ቅርንጫፍ ፖስታ ቤት በመገኘት የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን እና ሌሎች በቅርንጫፍ ፖስታ ቤቱ የተሰሩ ስራዎችን ጎብኝተዋል።

የአገልግሎቶቻችንን ምህዳር እና ጥራት በማሳደግ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ተጠቃሚነት እየሰራን ባለንበት በዚህ ወቅት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን እያደረጋችሁልን ስላለው ድጋፍ እናመሰግናለን!

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »