ኢትዮጵያ ፖስታ በመቄዶኒያ ላሉ ተረጂዎች የሚውል ከ300,000 ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁሶችን አስረክቧል።በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቢረዳ እንዲሁም የንብረት አስተዳደር ክፍል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ይፍቱስራ መኮንን መገልገያ ቁሳቁሶቹን ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያስረከቡ ሲሆን የመቄዶኒያ አረጋዉያን የቡራኬ ስነስርዓት አድርገዋል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ፖስታ ከ700,000 ብር በላይ የሚገመት የቢሮ መገልገያ እቃዎች ያስረከበ ሲሆን በቀጣይም የኢትዮጵያ ፖስታ ለመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኅበር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስገንዘበዋል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።
ይህ ስምምነት 700 በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፎች የሰነዶችን ምዝገባ አገልግሎትን እንዲያካሄድ የሚስችላቸው ነው።