የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን ከሰራተኞች ጋር በተለያዩ ከተሞች ለቀናት የቆየ ስብሰባ አድርጓል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ አመራር ቡድን ከሰራተኞች ጋር በድሬዳዋ፣ በደሴ፣ ሀዋሳ፣ በጅማ እና መቀሌ ከተሞች ለቀናት የቆየ ስብሰባ አድርጓል፡፡ በስብሰባው የድርጅቱን የሶስት አመታት ስትራቴጂ የማጋራት እና የግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማን መሪ አካል ያደረገ ነበር።  ስብሰባው  ተቋሙ አሁንም በልህቀት እና በቅልጥፍና ስራውን እንዲቀጥል የሚያበረታታ እንደነበር ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤት፣ አጠቃላይ ፖስታ ቤት እና የማዕከላዊ ወረዳ ቅርንጫፎች የግማሽ አመታዊ አፈፃፀምን በተመለከተ የተደረገው ስብስባ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።

በድሬዳዋ ከተማ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ከተደረገው ውይይት የተወሰዱ ምስሎች ።

በደሴ እና ሀዋሳ ከተማ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ከተደረገው ውይይት የተወሰዱ ምስሎች ።

በጅማ እና መቀሌከተማ ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር ከተደረገው ውይይት የተወሰዱ ምስሎች ።

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የአየር ኃይላችንን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጃቸውን አራት አይነት ታሪካዊ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።

ዛሬ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የተመሰረተበትን 90ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አክብሯል። የኢትዮጵያ ፖስታ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ ለመዘከር ያሳተማቸውን አራት አይነት ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፋ አስመርቋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በይፋ አስመረቀ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ያበለጸጋቸውን የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመርቋል፡፡

Read More »