Ethiopost welcomes Secretary General of PAPU

የፓን አፍሪካ ፖስታ ህብረት (PAPU) ዋና ፀሐፊ ለሆኑት ለክቡር ዶ/ር ሲፉንዶ ቺፍ ሞዮ ደማቅ አቀባበል ስናደርግላቸው በታላቅ ክብር ነው። በጉብኝታቸውም ወቅት የኢትዮጵያፖስታን እድገት በሚመለከት ገንቢ ውይይት አድርገን ለወደፊቱ የትብብር መንገዶችን ቃኝተናል። ጉብኝቱ የኢትዮጵያፖስታን አገልግሎቶችን አጠቃላይ ጉብኝት ያቀፈ ሲሆን ይህም ክቡር ዶ/ር ሲፉንዶ ቺፍ ሞዮ ስለአሰራራችን የሰፋ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አስችሏል። በተጨማሪም፣ ለፖስታ አገልግሎት ሰራተኞች ክፍት የሆነውን የልጆች ማቆያ አብረው ጎብኝተዋል።

ይህ ስብሰባ በ የኢትዮጵያፖስታ እና በፓን አፍሪካ ፖስታ ህብረት (PAPU) መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና ሀሳብ ለመለዋወጥ ጠቃሚ እድል ሰጥቷል።

Ethiopost is honored to extend a warm welcome to His Excellency Dr. Sifundo Chief Moyo, the Secretary General of the Pan African Postal Union (PAPU). During his visit, we had a constructive discussion on the trajectory of Ethiopost and explored potential avenues for collaboration in the future.

The visit encompassed a comprehensive tour of Ethiopost’s services, allowing H.E. Dr. Sifundo Chief Moyo to gain firsthand insights into our operations. Additionally, we had the privilege of showcasing the Ethiopost daycare facility, highlighting our commitment to the holistic well-being of our community.

We look forward to the prospect of future collaborations that will contribute to the advancement of postal services on both a national and continental scale.

More updates Ethiopost

News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር የመገልገያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ቢረዳ እንዲሁም የንብረት አስተዳደር ክፍል ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ይፍቱስራ መኮንን መገልገያ ቁሳቁሶቹን ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር ያስረከቡ ሲሆን የመቄዶኒያ አረጋዉያን የቡራኬ ስነስርዓት አድርገዋል።

Read More »
News

የ2024 የእስያ ፊላቴሊክ ኤግዚቢሽን በቻይና።

በሻንጋይ የተካሄደው የ2024 የኤዥያ አለም አቀፍ የቴምብር ኤግዚቢሽን የእስያን ባህል በፊላቴሊ ጥበብ የሚያሳይ ደማቅ በዓል ነበር። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎች አስደናቂውን የቴምብር ማሳያ አድንቀዋል፣ እያንዳንዱም የቴምብር ስራዎች ታሪክን፣ ጥበብን እና ወግን ይናገራሉ።

Read More »
News

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

በክቡር አቶ እውነቱ አለነ የተመራ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት እና የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ሁለንተናዊ ተሃድሶ እንዲሁም አጠቃላይ የስራ ክንውን ላይ ውይይት እና የመስክ ጉብኝት አካሂደዋል።

Read More »