Ethiopost welcomes Secretary General of PAPU

የፓን አፍሪካ ፖስታ ህብረት (PAPU) ዋና ፀሐፊ ለሆኑት ለክቡር ዶ/ር ሲፉንዶ ቺፍ ሞዮ ደማቅ አቀባበል ስናደርግላቸው በታላቅ ክብር ነው። በጉብኝታቸውም ወቅት የኢትዮጵያፖስታን እድገት በሚመለከት ገንቢ ውይይት አድርገን ለወደፊቱ የትብብር መንገዶችን ቃኝተናል። ጉብኝቱ የኢትዮጵያፖስታን አገልግሎቶችን አጠቃላይ ጉብኝት ያቀፈ ሲሆን ይህም ክቡር ዶ/ር ሲፉንዶ ቺፍ ሞዮ ስለአሰራራችን የሰፋ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አስችሏል። በተጨማሪም፣ ለፖስታ አገልግሎት ሰራተኞች ክፍት የሆነውን የልጆች ማቆያ አብረው ጎብኝተዋል።

ይህ ስብሰባ በ የኢትዮጵያፖስታ እና በፓን አፍሪካ ፖስታ ህብረት (PAPU) መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እና ሀሳብ ለመለዋወጥ ጠቃሚ እድል ሰጥቷል።

Ethiopost is honored to extend a warm welcome to His Excellency Dr. Sifundo Chief Moyo, the Secretary General of the Pan African Postal Union (PAPU). During his visit, we had a constructive discussion on the trajectory of Ethiopost and explored potential avenues for collaboration in the future.

The visit encompassed a comprehensive tour of Ethiopost’s services, allowing H.E. Dr. Sifundo Chief Moyo to gain firsthand insights into our operations. Additionally, we had the privilege of showcasing the Ethiopost daycare facility, highlighting our commitment to the holistic well-being of our community.

We look forward to the prospect of future collaborations that will contribute to the advancement of postal services on both a national and continental scale.

More updates Ethiopost

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

Read More »
News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »