በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ።

በጉብኝቱ ወቅት የኢትዮጵያ ፖስታ ለኢ-ኮሜርስ ሥራ እያደረገ ያለውን ዝግጁነት እና የተለያዩ የሥራ ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በቅርቡ ወደ ሥራ የሚገባውን የኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ ጨምሮ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎቱን በተሻለ ለማዘመን እየሰራቸው ባሉ ሥራዎች ዙሪያ በዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በድርጅቱ አመራሮች ለኮሚቴው ገለጻ ተደርጓል፡፡

በተመሳሳይ በውይይቱ ላይም የኢትዮጵያ ፖስታ ኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ የአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽ ለማድረግ ያለመ እና የንግድ ስርዓቱንም በማዘመን ሂደት ትልቅ አወንታዊ ሚና እንደሚኖረው የተነሳ ሲሆን፤ ኮሚቴው አጠቃላይ የንግድ ምህዳሩን ለኢ-ኮሜርስ ምቹ ከማድረግ አንጻር መሰራት በሚገባቸው ሥራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በመጨረሻም በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ይድነቃቸው ወልደተንሳይ እንዲሁም የኮሚቴው አባላት በጉብኝታቸው የተመለከቱት የኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ሥራ ዝግጅት አበረታች መሆኑን ገልጸው ተጠናክሮ መቀጠልና በሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎችም በተመሳሳይ ዝግጅት መደረግ እንዳለበት አንስተዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ የመታሰቢያ ቴምብሮች በይፉ አስመረቀች።

የኢትዮጵያ ፖስታ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅና ታሪካዊ እሴቶቻችንን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል። ይህንን ታላቅ ኩነት አስመልክቶ የወጣው ልዩ የመታሰቢያ ቴምብርም ተቋማችን የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ስኬት ለዓለም በማብሰር ረገድ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።

የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ መድረክ የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ተሸላሚ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፉ የፖስታ ህብረት (UPU) የፈጣን መልዕክት አገልግሎት (EMS) የ2025 የጥራት ምዘና ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ቀዳሚነቱን ሲያረጋግጥ፣ ከመላው ዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል።

Read More »
News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »