በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተመራው የብሔራዊ ኢ-ኮሜርስ ኮሚቴ ልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት እና ውይይት አደረገ።

በጉብኝቱ ወቅት የኢትዮጵያ ፖስታ ለኢ-ኮሜርስ ሥራ እያደረገ ያለውን ዝግጁነት እና የተለያዩ የሥራ ክፍሎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በቅርቡ ወደ ሥራ የሚገባውን የኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ ጨምሮ በቀጣይ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎቱን በተሻለ ለማዘመን እየሰራቸው ባሉ ሥራዎች ዙሪያ በዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና በድርጅቱ አመራሮች ለኮሚቴው ገለጻ ተደርጓል፡፡

በተመሳሳይ በውይይቱ ላይም የኢትዮጵያ ፖስታ ኢ-ኮሜርስ መተግበሪያ የአነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ለዓለም አቀፍ ገበያ ተደራሽ ለማድረግ ያለመ እና የንግድ ስርዓቱንም በማዘመን ሂደት ትልቅ አወንታዊ ሚና እንደሚኖረው የተነሳ ሲሆን፤ ኮሚቴው አጠቃላይ የንግድ ምህዳሩን ለኢ-ኮሜርስ ምቹ ከማድረግ አንጻር መሰራት በሚገባቸው ሥራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በመጨረሻም በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ይድነቃቸው ወልደተንሳይ እንዲሁም የኮሚቴው አባላት በጉብኝታቸው የተመለከቱት የኢትዮጵያ ፖስታ የኢ-ኮሜርስ ሥራ ዝግጅት አበረታች መሆኑን ገልጸው ተጠናክሮ መቀጠልና በሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎችም በተመሳሳይ ዝግጅት መደረግ እንዳለበት አንስተዋል፡፡

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »