በዛሬው ዕለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ጉብኝት እና ውይይት አደረጉ። ውይይቱ በዋነኝነት የኢትዮጵያ ፖስታ አሁን ያለበትን ደረጃ ካለው ሰራተኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሃላፊዎች ድረስ ያለውን እይታ የቃኘ ነበር። በተጨማሪም ከጉብኝቱ እንደተገነዘቡት የኢትዮጵያ ፖስታ በሁሉም መስክ በሚባል ደረጃ አመርቂ ለውጥ እያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ከሰራተኛው በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ከሃላፊዎች ማብራርያ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ለመቄዶኒያ አበረከተ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት አንድ አካል አድርጎ በተለያዩ ዙሮች ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡













