በዛሬው ዕለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ጉብኝት እና ውይይት አደረጉ። ውይይቱ በዋነኝነት የኢትዮጵያ ፖስታ አሁን ያለበትን ደረጃ ካለው ሰራተኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሃላፊዎች ድረስ ያለውን እይታ የቃኘ ነበር። በተጨማሪም ከጉብኝቱ እንደተገነዘቡት የኢትዮጵያ ፖስታ በሁሉም መስክ በሚባል ደረጃ አመርቂ ለውጥ እያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ከሰራተኛው በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ከሃላፊዎች ማብራርያ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።
የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።













