በዛሬው ዕለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዮች በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ጉብኝት እና ውይይት አደረጉ። ውይይቱ በዋነኝነት የኢትዮጵያ ፖስታ አሁን ያለበትን ደረጃ ካለው ሰራተኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ሃላፊዎች ድረስ ያለውን እይታ የቃኘ ነበር። በተጨማሪም ከጉብኝቱ እንደተገነዘቡት የኢትዮጵያ ፖስታ በሁሉም መስክ በሚባል ደረጃ አመርቂ ለውጥ እያስመዘገበ መሆኑን ጠቅሰው ከሰራተኛው በኩል ለተነሱ ጥያቄዎች ከሃላፊዎች ማብራርያ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቅቋል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቀረበ።
የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት የ2018 በጀት ዓመት የ 9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቅርቦ አስገመገመ።












