የኢትዮጵያ ፖስታ 131ኛ ዓመት የምስረታ በዓል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ላለፉት 131 ዓመታት በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ግንባር ቀደም የግንኙነት ምሰሶ በመሆን ሰዎችን ከሰዎች ተቋማትን ከተቋማት በማገናኘት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ባህላዊ ትስስር እንዲጠነክርና የንግድ ልውውጥ እንዲያድግ የበኩሉን አስተዋፅዖ ሲያበረክት የቆየ አንጋፋ የህዝብ ተቋም ነው።

በቀድሞ ጊዜ ከነበረው የፖስታ ልውውጥ አሰራር አንስቶ እስከ አሁኑ ዘመናዊ የሎጂስቲክስና የዲጂታል ዘመን ከሁኔታዎችና ወቅታዊ ፍላጐቶች ጋር እራሱን በማስተዋወቅና በማዘመን እንዲሁም የአገልግሎት አድማሱንና ተደራሽነቱን በማስፋት ላለፉት አንድ መቶ ሠላሣ አንድ ዓመታት በትጋትና በአገልጋይነት መንፈስ ተጉዟል።

ዛሬም ይህን ትውልዶች የተቀባበሉትን አስደናቂ ምዕራፍ 131ኛ የምስረታ በዓል ስናከብር የዚህ ጉዞ አካል የሆኑትን ውድ ሰራተኞቻችንን፣ ውድ ደንበኞቻችንን እና አጋሮቻችንን በማመስገንና ላበረከቱት አስተዋፅዖ እውቅና በመስጠት ነው።

በቀጣይም አኩሪ የሕዝብ አገልጋይነት ታሪካችንን ሰንቀን ያሁኑንና ቀጣዩን ትውልድ ለማገልገል ይረዳን ዘንድ ቴክኖሎጂን በማቀፍ፣ አዳዲስ የአሰራር ስልቶችን በመንደፍና የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል በማድረግ ሁሌም ከትናንቱ በተሻለ ልናገለግልዎ ዝግጁ መሆናችንን በመግለጽ ነው።

መልካም 131ኛ ዓመት!

More updates Ethiopost

News

የ2017 ዓ.ም አጠቃላይ አገር አቀፍ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ገለጻ ለኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኞች ተደረገ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የኘላንና ልማት ሚኒስቴር ቢሮ ያወጣውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ ለሰራተኞች አጠቃላይ በተለያዪ ዘርፎች የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ላይ ገለጻ አድርገዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከፍተኛ የስራ አመራሮች የኢትዮጵያ ፖስታን ጎበኙ።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከፍተኛ የስራ አመራሮች በዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ እና በምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ኃ/ሚካኤል የተመራ ከፍተኛ የስራ አመራሮች ልዑክ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና መስሪያ ቤትን የጎበኙ ሲሆን በድርጅቱ የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ላይ ስትራቴጂካዊ ውይይት አድርገዋል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 131ኛ ዓመት የምስረታ በዓል።

በቀድሞ ጊዜ ከነበረው የፖስታ ልውውጥ አሰራር አንስቶ እስከ አሁኑ ዘመናዊ የሎጂስቲክስና የዲጂታል ዘመን ከሁኔታዎችና ወቅታዊ ፍላጐቶች ጋር እራሱን በማስተዋወቅና በማዘመን እንዲሁም የአገልግሎት አድማሱንና ተደራሽነቱን በማስፋት ላለፉት አንድ መቶ ሠላሣ አንድ ዓመታት በትጋትና በአገልጋይነት መንፈስ ተጉዟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።

Read More »