የኢትዮጵያ ፖስታ 131ኛ ዓመት የምስረታ በዓል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ላለፉት 131 ዓመታት በኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ግንባር ቀደም የግንኙነት ምሰሶ በመሆን ሰዎችን ከሰዎች ተቋማትን ከተቋማት በማገናኘት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ባህላዊ ትስስር እንዲጠነክርና የንግድ ልውውጥ እንዲያድግ የበኩሉን አስተዋፅዖ ሲያበረክት የቆየ አንጋፋ የህዝብ ተቋም ነው።

በቀድሞ ጊዜ ከነበረው የፖስታ ልውውጥ አሰራር አንስቶ እስከ አሁኑ ዘመናዊ የሎጂስቲክስና የዲጂታል ዘመን ከሁኔታዎችና ወቅታዊ ፍላጐቶች ጋር እራሱን በማስተዋወቅና በማዘመን እንዲሁም የአገልግሎት አድማሱንና ተደራሽነቱን በማስፋት ላለፉት አንድ መቶ ሠላሣ አንድ ዓመታት በትጋትና በአገልጋይነት መንፈስ ተጉዟል።

ዛሬም ይህን ትውልዶች የተቀባበሉትን አስደናቂ ምዕራፍ 131ኛ የምስረታ በዓል ስናከብር የዚህ ጉዞ አካል የሆኑትን ውድ ሰራተኞቻችንን፣ ውድ ደንበኞቻችንን እና አጋሮቻችንን በማመስገንና ላበረከቱት አስተዋፅዖ እውቅና በመስጠት ነው።

በቀጣይም አኩሪ የሕዝብ አገልጋይነት ታሪካችንን ሰንቀን ያሁኑንና ቀጣዩን ትውልድ ለማገልገል ይረዳን ዘንድ ቴክኖሎጂን በማቀፍ፣ አዳዲስ የአሰራር ስልቶችን በመንደፍና የደንበኞችን ፍላጎት ማዕከል በማድረግ ሁሌም ከትናንቱ በተሻለ ልናገለግልዎ ዝግጁ መሆናችንን በመግለጽ ነው።

መልካም 131ኛ ዓመት!

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »