የኢትዮጵያ ፖስታ ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ። የመግባቢያ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ እና የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃሚድ ኪኒሶ መካከል ተፈርሟል። ይህ ስምምነት 700 በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፎች የሰነዶችን ምዝገባ አገልግሎትን እንዲያካሄድ የሚስችላቸው ሲሆን ይህም በተደራሽነት ፣ ወጥነት ያለው የክፍያ አሰራርን ከመዘርጋት አኳያ እና ሙያዊ ስነምግባርን የተላበሰ አገልግሎት ከመስጠት አንጳር ትልቅ እምርታ ያመጣል ተብሎ ይታመናል። ይህም አገልግሎት በጥቂት ሳምንታት ውስጥ በተመረጡ የኢትዮጵያ ፖስታ ቅርንጫፎች ውስጥ መሰጠት ይጀምራል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከ1.4 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ ለመቄዶኒያ አበረከተ።
የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት አንድ አካል አድርጎ በተለያዩ ዙሮች ለመቄዶኒያ የአረጋውያን እና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል፡፡












