የ2017 ዓ.ም አጠቃላይ አገር አቀፍ የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ገለጻ ለኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኞች ተደረገ።

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የኘላንና ልማት ሚኒስቴር ቢሮ ያወጣውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ ለሰራተኞች አጠቃላይ በተለያዪ ዘርፎች የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ላይ ገለጻ አድርገዋል። ይህንንም ተከትሎ በቀረበውም ሪፖርት ላይ በታየውን አበራታች ውጤት ሰራተኞች መልካም አስተያየቶችን ሰተውበታል። በቀጣይም የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል፣ በተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎች እና መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ልዪ ትኩረት በማድረግና በጋራ በመረባረብ ለበለጠ ውጤት ለመትጋት በመስማማት ውይይቱ ተጠናቋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በአሐዱ ባንክ መካከል በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ በአገልግሎት ማስፋፋት እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚደረጉ ትብብሮችን በማጠናከር ለህብረተሰቡ የቀረበ እና ዘመናዊ አገልግሎት ለማቅረብ እየሠራ ባለው ሥራ ላይ ይህ የስምምነት ፊርማ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከM-PESA ኢትዮጵያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ፖስታ ከ M-PESA ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ 1000 በላይ ቅርንጫፎች አማካይነት የM-PESA አገልግሎትን እንደ ዋና ወኪል በመሆን ለደንበኞቹ ማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን አከበረ፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ለመላው የኢትዮጵያ ፖስታ ማህበረሰብ ለኢትዮጵያ ፖስታ 132ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እንዲሁም ለዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጉብኝት አካሄዱ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ጉብኝቱ ላይ ባዩዋቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እየተሰሩ ባሉት ሥራዎች ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

Read More »