በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የኘላንና ልማት ሚኒስቴር ቢሮ ያወጣውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ ለሰራተኞች አጠቃላይ በተለያዪ ዘርፎች የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ላይ ገለጻ አድርገዋል። ይህንንም ተከትሎ በቀረበውም ሪፖርት ላይ በታየውን አበራታች ውጤት ሰራተኞች መልካም አስተያየቶችን ሰተውበታል። በቀጣይም የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል፣ በተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎች እና መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ልዪ ትኩረት በማድረግና በጋራ በመረባረብ ለበለጠ ውጤት ለመትጋት በመስማማት ውይይቱ ተጠናቋል።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ስምምነት ተፈራረሙ።
የኢትዮጵያ ፖስታ እና የኢትዮ ላይፍ ኤንድ ጄኔራል ኢንሹራንስ ኩባንያ “ልባም” የተሰኘውን የዲጂታል የህይወት መድን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።













