በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የኘላንና ልማት ሚኒስቴር ቢሮ ያወጣውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ ለሰራተኞች አጠቃላይ በተለያዪ ዘርፎች የ2017 ዓ.ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ላይ ገለጻ አድርገዋል። ይህንንም ተከትሎ በቀረበውም ሪፖርት ላይ በታየውን አበራታች ውጤት ሰራተኞች መልካም አስተያየቶችን ሰተውበታል። በቀጣይም የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል፣ በተቀመጡ የትኩረት አቅጣጫዎች እና መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ልዪ ትኩረት በማድረግና በጋራ በመረባረብ ለበለጠ ውጤት ለመትጋት በመስማማት ውይይቱ ተጠናቋል።
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡













