የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ ቴምብር ተሰራለት፡፡

በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደው የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ያሳተማቸውን ቴምብሮች አስመርቋል፡፡

በዝግጅቱ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ እና ዲፕሎማት ዶ/ር ተቀዳ ዓለሙ ፣የቀድሞ የትምህርት ሚኒስቴር ዶ/ር ያየህይራድ ቅጣው፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የካፍ ሥራ አስፈጻሚ እና የፊፋ ጸረ-ዘረኝነትና ጸረ-አግላይነት ኮሚቴ አባል አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የኢ/እ/ፌ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን፣ የመንግሥቱ ወርቁ መታሰብያ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰሎሞን በቀለ፣ የመጽሐፉ ጸሐፊ ዶ/ር ሰሎሞን በርኼ፣ የቀድሞ ተጫዋች፣ የኮሚቴ አባላት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የመገናኛ ብዙሀን አካላት በተገኙበት የቴምብር ስራዎች እንዲሁም በስፖርተኛው ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ተመርቋል፡፡

በተያያዘም የኢትዮጵያ ፖስታ ከቴምብር ሥራዎች ጀምሮ ለዝግጅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ዋንጫ የተበረከተለት ሲሆን ከመድረኩም ታላቅ ምስጋና ተችሮታል፡፡

በመጨረሻም የታላቁ የእግር ኳስ ሰው የመንግሥቱ ወርቁን ቤተሰብ በመወከል ንግግር ያደረጉት ፓስተር እሸቴ በቀለ እንደ አጠቃላይ የትኢዮጵያ ፖስታን ጨምሮ ታላላቅ የሀገር ባለውለታዎች እና ባለአደራዎች ይህን መርሐ ግብር በማዘጋጀታቸው በቤተሰብ ስም በማመስገን ስለ መንግሥቱ ወርቁ በስንኝ የታጀበ ምስክርነት አቅርበዋል።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »