በኃይሌ ግራንድ ሆቴል በተካሄደው የታላቁ የእግር ኳስ ሰው መንግሥቱ ወርቁ የመታሰብያ መርሐ ግብር ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ያሳተማቸውን ቴምብሮች አስመርቋል፡፡
በዝግጅቱ ላይም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዴኤታ እና ዲፕሎማት ዶ/ር ተቀዳ ዓለሙ ፣የቀድሞ የትምህርት ሚኒስቴር ዶ/ር ያየህይራድ ቅጣው፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት የካፍ ሥራ አስፈጻሚ እና የፊፋ ጸረ-ዘረኝነትና ጸረ-አግላይነት ኮሚቴ አባል አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የኢ/እ/ፌ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን፣ የመንግሥቱ ወርቁ መታሰብያ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰሎሞን በቀለ፣ የመጽሐፉ ጸሐፊ ዶ/ር ሰሎሞን በርኼ፣ የቀድሞ ተጫዋች፣ የኮሚቴ አባላት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የመገናኛ ብዙሀን አካላት በተገኙበት የቴምብር ስራዎች እንዲሁም በስፖርተኛው ላይ ያተኮረ መጽሐፍ ተመርቋል፡፡
በተያያዘም የኢትዮጵያ ፖስታ ከቴምብር ሥራዎች ጀምሮ ለዝግጅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ዋንጫ የተበረከተለት ሲሆን ከመድረኩም ታላቅ ምስጋና ተችሮታል፡፡
በመጨረሻም የታላቁ የእግር ኳስ ሰው የመንግሥቱ ወርቁን ቤተሰብ በመወከል ንግግር ያደረጉት ፓስተር እሸቴ በቀለ እንደ አጠቃላይ የትኢዮጵያ ፖስታን ጨምሮ ታላላቅ የሀገር ባለውለታዎች እና ባለአደራዎች ይህን መርሐ ግብር በማዘጋጀታቸው በቤተሰብ ስም በማመስገን ስለ መንግሥቱ ወርቁ በስንኝ የታጀበ ምስክርነት አቅርበዋል።















