የኢትዮጲያ ፖስታ ከመንግስት፣ ከፋይናንሺያል አገልግሎት ሰጪዎች እና ከሞባይል ኔትወርክ ኦፕሬተሮች ጋር በመተባበር የገንዘብ ነክ የሆኑ እና ያልሆኑ አገልግሎቶችን በመላው ኢትዮጵያ እያሳደገ ይገኛል። አላማችን የእርስዎ ተመራጭ የአገልግሎት መዳረሻ አጋር መሆን ነው። በቅርቡ በኡጋንዳ ከኢትዮጲያ ፖስታ ቡድን ጋር የተደረገ የእውቀት ልውውጥ ጉብኝት አዳዲስ ግንዛቤዎችን ፈጥሯል፣ ለዚህም Amarante Consulting እና Bill and Melinda Gates Foundation ስለ ድጋፋቸው እናመሰግናለን። Posta Uganda Limited፣ Uganda Bankers’ Association፣ Financial Sector Deepening Uganda (FSD Uganda)፣ Agent Banking Company፣ MTN Uganda PostBank Uganda Ltd፣ እና Interswitch Groupን ጨምሮ ለኡጋንዳ አጋሮቻችን የጋራ ራዕይ ብሎም ስላደረጉልን መልካም እንግዳ ተቀባይነት ከልብ እናመሰግናለን።
የኢትዮጵያ ፖስታ በዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን የሙዚየም ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተበረከተለት።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሙዚየም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ “የተከፋፈለችውን ዓለም የሚያስተሳስሩ ሙዚየሞች” በሚል እጅግ ወቅታዊ መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ በረከት ዘውዴ እና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡





