የኢትዮጲያ ፖስታ ገንዘብ ነክ የሆኑ እና ያልሆኑ አገልግሎቶችን በመላው ኢትዮጵያ እያሳደገ ይገኛል።

የኢትዮጲያ ፖስታ ከመንግስት፣ ከፋይናንሺያል አገልግሎት ሰጪዎች እና ከሞባይል ኔትወርክ ኦፕሬተሮች ጋር በመተባበር የገንዘብ ነክ የሆኑ እና ያልሆኑ አገልግሎቶችን በመላው ኢትዮጵያ እያሳደገ ይገኛል። አላማችን የእርስዎ ተመራጭ የአገልግሎት መዳረሻ አጋር መሆን ነው። በቅርቡ በኡጋንዳ ከኢትዮጲያ ፖስታ ቡድን ጋር የተደረገ የእውቀት ልውውጥ ጉብኝት አዳዲስ ግንዛቤዎችን ፈጥሯል፣ ለዚህም Amarante Consulting እና Bill and Melinda Gates Foundation ስለ ድጋፋቸው እናመሰግናለን። Posta Uganda Limited፣ Uganda Bankers’  Association፣ Financial Sector Deepening Uganda (FSD Uganda)፣ Agent Banking Company፣ MTN Uganda PostBank Uganda Ltd፣ እና Interswitch Groupን ጨምሮ ለኡጋንዳ አጋሮቻችን የጋራ ራዕይ  ብሎም ስላደረጉልን መልካም እንግዳ ተቀባይነት ከልብ እናመሰግናለን።

More updates Ethiopost

News

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና  በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ  ተፈራርመዋል፡፡

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።

በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

Read More »
News

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።

በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።

Read More »