የኢትዮጲያ ፖስታ ከመንግስት፣ ከፋይናንሺያል አገልግሎት ሰጪዎች እና ከሞባይል ኔትወርክ ኦፕሬተሮች ጋር በመተባበር የገንዘብ ነክ የሆኑ እና ያልሆኑ አገልግሎቶችን በመላው ኢትዮጵያ እያሳደገ ይገኛል። አላማችን የእርስዎ ተመራጭ የአገልግሎት መዳረሻ አጋር መሆን ነው። በቅርቡ በኡጋንዳ ከኢትዮጲያ ፖስታ ቡድን ጋር የተደረገ የእውቀት ልውውጥ ጉብኝት አዳዲስ ግንዛቤዎችን ፈጥሯል፣ ለዚህም Amarante Consulting እና Bill and Melinda Gates Foundation ስለ ድጋፋቸው እናመሰግናለን። Posta Uganda Limited፣ Uganda Bankers’ Association፣ Financial Sector Deepening Uganda (FSD Uganda)፣ Agent Banking Company፣ MTN Uganda PostBank Uganda Ltd፣ እና Interswitch Groupን ጨምሮ ለኡጋንዳ አጋሮቻችን የጋራ ራዕይ ብሎም ስላደረጉልን መልካም እንግዳ ተቀባይነት ከልብ እናመሰግናለን።

News
የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲቱት ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
ይህ አጋርነት ዘመናዊ የካርታ አሰራርን በኢትዮጵያ ፖስታ ሎጅስቲክስ ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን እና ጥራትን ለማሳደግ ያለመ ነው:: ይህንን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ፈጣን እና አስተማማኝ የቤት ለቤት እደላ አገልግሎትን በማሳለጥ የደንበኞችን እርካታን ማሻሻል ይቻላል።