News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን በይፋ አስመረቀ፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ያበለጸጋቸውን የ ሳጥን አልባ መልዕክት አገልግሎት እንዲሁም የፖስታ ገበያ መተግበሪያዎችን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ባለቤቶች በተገኙበት በስካይ ላይት ሆቴል በይፋ አስመርቋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።
የኢትዮጵያ ፖስታ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል የሰራቸውን የቴምብር ሥራዎች በይፋ አስመርቋል።

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውል ተፈረመ፡፡
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፖስታን በመወከል ወ/ሮ ትዕግስት በቀለ ቺፍ ኮሜርሻል ኦፊሰር እና በእልባት ማኔጅመንት እና ቴክኖሎጂ ሶሉሽን በኩል ደግሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ነፃነት ራያ ተፈራርመዋል፡፡

የሩሲያው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ በኢትዮጵያ ፖስታ ጉብኝት አደረገ።
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አስተባባሪነት መቀመጫውን ሩሲያ ላይ ያደረገው የኢ-ኮሜርስ ኩባንያ ‘’RWB’’ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ፖስታ ተገኝተው ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከኢት-ስዊች አክሲዮን ማሕበር ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ።
በስምምነት ፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ እና ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የተፈራረሙት ስምምነት የኤጀንት ኔትወርክ ማኔጅመንት መተግበሪያን በጋራ ለማበልፀግ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

አዲስ የተሾሙት የኢትዮጵያ ፖስታ የቦርድ አባላት በተቋሙ ውስጥ ጉብኝት አድርገዋል፡፡
ባለፉት ሶስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፖስታን ሲያገለግል በቆየው ቦርድ የተተካው አዲሱ ቦርድ አመራር አባላት በተቋሙ ውስጥ በመገኘት በሁሉም የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው ጉብኝት አድርገዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ነባር የቦርድ አባላት የሽኝት እና ለአዲሱ ቦርድ አባላት የአቀባበል ስነስርአት ተካሄደ።
በሽኝት ሥነሥርዓቱ ላይ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የተቋሙ የስትራቴጂ እቅድ ግቡን እንዲመታ የቦርድ አባላቱ ያበረከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በማንሳት በኢትዮጵያ ፖስታ ውስጥ ትልቁን ታሪክ እንደፃፉ እና ትልቅ ምስጋና እና ክብር እንደሚገባቸው ገልፀዋል።
