News and Updates from Ethiopost
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መልእክት።
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልእክታቸው ላይ የግድቡ መጠናቀቅ እንደ ሃገር

የኢትዮጵያ ፖስታ በደንበኞች አገልግሎት ጥራት ተሸላሚ ሆነ።
የአለም አቀፉ የፖስታ ህብረት 28ኛው ጠቅላላ ጉባዬ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ ባሳየው የላቀ አፈፃፀም የ2024 የፈጣን መልእክት የደንበኞች አገልግሎት ጥራት ሽልማትን ተቀብሏል።

በኢትዮጵያ ፖስታ እና በቲና ማርት መካከል የጋራ መግባቢያ ሠነድ ተፈረመ።
የኢትዮጵያ ፖስታ በኦን ላይን የግብይት ስርዓቱ ላይ በአጭር ግዜ ውስጥ ትልቅ ልዩነትን እየፈጠረ ከሚገኘው ቲና ማርት ጋር አብሮ የመስራት ስምምነት ተፈራርሟል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ ላለፉት ተከታታይ አመታት በተሰሩት የሪፎርም ስራዎች ላይ ተመስርቶ ‹‹በጥልቀት እና በስፋት›› በሚል ስትራቴጂክ ፕላን ተቋሙን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተሰራ ያለው ስራ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም 50ኛ ዓመት የወርቅ እዩ ቤልዩ ክብረ በዓል!
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳግማዊ ኃይልዬ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን እንደተቋም የፖስታ ሙዚየሙ ላይ እየተሠሩ ያሉ የማስፋፊያ ሥራዎች እንዳሉ እና በቅርቡ ይፋ እንደሚደረጉ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጉብኝት፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንጦጦ በሚገኘው የስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና የምርምር ማዕከልን ጎበኙ፡፡

የኢትዮጵያ ፖስታ የሥራ አመራሮች የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም እቅዶች ላይ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አደረጉ።
በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፖስታ የአቅርቦት እና ፋሲሊቲ ቺፍ ኦፊሰር የሆኑት አቶ ጋሻው መርሻ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገዋል፤ አያይዘውም በ2017 በጀት ዓመት ለነበረው አፈጻጸም ሁሉም የኢትዮጵያ ፖስታ ሰራተኛ ምስጋና ሊቸረው እንደሚገባ አንስተው በቀጣይም ይኸው የሥራ መነሳሳት እና ተልዕኮዎቻችንን በድል የመወጣት ባሕል ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡